የምስራቅ አፍሪቃ የአንበጣ መከላከያ 50ኛ አመት
ማክሰኞ፣ መስከረም 8 2005ማስታወቂያ
DLCO በመባል የሚታወቀዉ የምስራቅ አፍሪቃ አንበጣ መከላከያ ድርጅት የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት አዲስ አበባ ላይ እያከበረ ይገኛል። ስምንት የአፍሪቃ አገራትን ያካተተዉ ይህ ድርጅት ቀደም ባለዉ ግዜ የመድሃኒት መርጫ አዉሮፕላኖች እጥረት እንደነበረበት ይታወቃል። ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት ይህንን ችግሩን እንዴት በመፍታት ላይ ይገኛል? ኢትዮጵያ በድርጅቱ አኳያ ያላት ድርሻና ጥቅም ምን ይመስላል? የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ እና በኢትዮጵያ የግብርና እና ገጠር ልማት ሚንስቴር ሚንስትር ዴታ በዚሁ ጉዳይ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሃ/ጊዮርጊስ ተከታትሎታል።
ጌታቸዉ ተድላ ሃ/ጊዮርጊስ
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ