የምርጫ ዉጤትና ተቃዋሚ ፓርቲዎች
ረቡዕ፣ ሰኔ 17 2007ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) እና ተባባሪዎቹ ባለፈዉ ግንቦት በተደረገዉ ምርጫ ሙሉ በሙሉ አሸንፈዋል መባሉን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ማጣጣላቸዉን እንደቀጠሉ ነዉ።ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፈዉ ሰኞ ይፋ ባደረገዉ ዉጤት መሠረት ኢሕአዴግ እና ተባባሪዎቹ የብሔራዊዉንም፤ የክልልም ምክር ቤቶች መቀመጫዎች ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥረዉታል።የተቃዋሚ ፓርቲዎች መሪዎች እንደሚሉት የምርጫዉ ሒደትም ሆነ ዉጤቱ በኢሕአዲግ ቁጥጥር ሥር የተከናወነ ነበር።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ አራት የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን አነጋግሮ የሚከተለዉ ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሠ