የሚናው አደጋ እና አደናጋሪው የሟች ሀጃጆች ቁጥር12 ጥቅምት 2008ዓርብ፣ ጥቅምት 12 2008በሳውዲ አረቢያዋ ከተማ መካ አቅራቢያ በምትገኘው በሚና እአአ ባለፈው መስከረም 24፣ 2015 ዓም በተከሰተው መጨናነቅ እና ግፊያ ሰበብ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 769 መድረሱን የሳውዲ ዐረቢያ ባለስልጣናት በይፋ ከገለጹ ጥቂት ጊዜ አልፏል።https://p.dw.com/p/1GtLeምስል Getty Images/AFP/STRማስታወቂያ[No title]To play this audio please enable JavaScript, and consider upgrading to a web browser that supports HTML5 audio ከዚያን ጊዜ ወዲህ ግን የውጭ ሃገራት መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት፣ የማቾች ቁጥር ቢያንስ ወደ 2,200 ከፍ ብሏል። በአሁኑ ጊዜ የሳውዲ መንግሥት የአስከሬን መለየትን ስራ በማካሄድ ላይ መሆኑን አመልክቶዋል። የሟቾችን ቁጥር በተመለከተ ከሳውዲ በኩል በይፋ ምን እየተባለ መሆኑን በጄዳ የሚገኘውን ጋዜጠኛ ነቢዩ ሲራክን በስልክ ጠይቄው ነበር። አርያም ተክሌ አዜብ ታደሰ