የሙንሽኑ ገንዘብ አሳታሚ ድርጅት እና ከሙጋቤ ጋር ያለዉ ልዩ ወዳጅነት
ቅዳሜ፣ መጋቢት 20 2000ማስታወቂያ
ቀድሞ በኢኮኖሚ እድገትዋ በአፍሪቃ ተጠቃሽ የነበረችዉ ዝንባቤ፣ ዛሪ ሊነገር በሚያዳግተዉ የገንዘብ ግሽፈት ዉስጥ በመዘፈቅዋ፣ ለምርጫዉ መሰናዶ ደጋፊዎችን ለመመስብ እንዲያስችል ገንዘብ ማሳተሟን ቀጥላለች። ታድያ ይህ አምባ ገነን መንግስት በገንዘብ ህትመት ለአመታት በመርዳት ላይ ያለዉ በጀርመን በሙንሽን ከተማ የሚገኘዉ ማተምያ ቤት መሆኑ ነገሩን አስገራሚ አድርጎታል። Giesecke & Devrient የተሰኘዉ የሙንሽኑ ማተምያ ቤት እና የዝንባቤ መንግስት ወዳጅነት የጀመሩት በ 70 ዎቹ አመታት በዝንባቤ የነበረዉ የ ስሚዝ መንግስት ከወደቀ ወድያ መሆኑ ታዉቆአል። የዶቸ-ቬለዉ ሉድገር ሻዶምስኪ ዝርዝር ዘገባዉን አጠናቅሮታል። አዜብ ታደሰ እንዲህ ታቀርበዋለች።