1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት 100ኛ ዓመት መታሰቢያ

እሑድ፣ ሐምሌ 27 2006

የጀርመኑ ፕሬዚዳንት ዮአሂም ጋውክ እና የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ፍራንስዋ ኦሎንድ ከ100 ዓመት በፊት የዓለም ጦርነት ያስነሳውን ቀን በአንድነት አስበው ዋሉ።

https://p.dw.com/p/1CoBT
ምስል Reuters

ልክ በዛሬው ቀን እሁድ፣ እንደ እጎአ ሐምሌ 3 ቀን፣ 2014 ነበር ጀርመን በፈረንሳይ ላይ ጦርነት እንደምትከፍት ያወጀችው። ሁለቱ የጀርመን እና የፈረንሳይ ባለስልጣናት ዛሬ በምስራቅ ፈረንሳይ ሐርትማንስቫይለርኮፍ በሚባለው ቦታ ኤልሳስ ውስጥ ተገኝተው የመታሠቢያ የአበባ ጉንጉን አኑረዋል። እጎአ ከ1914 -1918 ዓም የ1ኛው የዓለም ጦርነት በተካሄደው ከባድ ውጊያ ወደ 30,000 የሚጠጉ የፈረንሳይ እና የጀርመን መታደሮች ሕይወት ጠፍቷል። በእዚህ የዛሬው የመታሰቢያ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙ 100 የፈረንሳይ እና የጀርመን ወጣቶች በዓለም ዙሪያ ዘረኝነትን እናጥፋ የሚል የሰላም መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዚዳንት ዮአሂም ጋውክ እና ፕሬዚዳንት ፍራንስዋ ኦሎንድ
ፕሬዚዳንት ዮአሂም ጋውክ እና ፕሬዚዳንት ፍራንስዋ ኦሎንድምስል AFP/Getty Images

የጀርመኑ ፕሬዚዳንት በአበባ ጉንጉን ማኖሩ ስነ-ስርዓት ወቅት፤ «ሰው በላው» የተሰኘው ተራራ ጦርነቱ የተካሄደበት ዘመን ትርጉም አልባ እና አሰቃቂ ሁናቴን እንደሚያመላክቱ ጥቂት ቦታዎች ሁሉ ተምሳሌት ነው ብለዋል። የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት በበኩላቸው በስነ-ስርዓቱ ወቅት፤ «አውሮጳ ጦርነቱን ድል ለመንሳት ተሳክቶለታል» ሲሉ ተደምጠዋል።

የጀርመን እና የፈረንሳይ ዕርቀ-ሠላም እና ወዳጅነት ለበርካታ የዓለማችን ክፍሎች አብነት ሊሆን የሚችል ነው ተብሏል።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ልደት አበበ