የመድረክ ልዑካን በባሕር-ማዶ ጉዞ30 መጋቢት 2002ሐሙስ፣ መጋቢት 30 2002መድረክ በመባል የሚታወቀው ስምንት የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የጠቀለለው ዋነኛ ተቃዋሚ ድርጅት ልዑካን ሰሞኑን በአሜሪካና በአውሮፓ እየተዘዋወሩ ለኢትዮጵያውያን ገለጻ ያደርጋሉ።https://p.dw.com/p/MqaUምስል AP Graphics/DW Fotomontageማስታወቂያከፍተኛው የልዑካን ቡድን በኢንጂነር ግዛቸው ሺፈራው፣ በዶር/ነጋሶ ጊዳዳና በአቶ ገብሩ አሥራት የሚመራ ሲሆን በኢትዮጵያ ምርጫና የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ለመወያየት በአሜሪካ መንግሥትና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተጋበዘ መሆኑም ተጠቅሷል። የአዲስ አበባ ወኪላችን ታደሰ እንግዳው በጉዞው ዋዜማ ትናንት እንጂነር ግዛቸው ሺፈራውን አነጋግሮ ነበር። ታደሰ እንግዳው መስፍን መኮንን ነጋሽ መሐመድ