1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የመላው አፍሪቃ የንግድ ምክር ቤት እና የአፍሪቃ ኤኮኖሚ

ሰኞ፣ ሰኔ 29 2001

ዓለም አቀፉ የኤኮኖሚ ቀውስ የአፍሪቃን ኤኮኖሚ እንዳይጎዳ በአፍሪቃ ህብረትና በመሪዎች ደረጃ አንድ ወሳኝ መፍትሄ እንዲገኝለት ተጠየቀ።

https://p.dw.com/p/IiIS
ምስል DW /Maya Dreyer

ይህ ካልሆነ ከመዳከም አልፎ ያልተጠበቀ ቀውስ ውስጥ ሊገባ ይችላል ሲሉ ዛሬ በአዲስ አበባ ስብሰባ ያካሄዱት የመላው አፍሪቃ የንግድ ምክር ቤት ተወካዮች አስጠነቀቁ። ካለፉት ሁለት ዓመት ወዲህ ማከራከር በያዘው የምክር ቤቱ ጽህፈት ቤት ከካይሮ ግብጽ ወደ አዲስ አበባ ይዛወር በሚል በተሰማው ጥያቄ ላይ ተወካዮቹ መክረው እንደሚወስኑ ተስፋ ተደርጓል።

ታደሰ እንግዳው/አርያም ተክሌ

ነጋሽ መሐመድ