የሕፃናት ትምሕርት በኢትዮጵያ
ረቡዕ፣ መስከረም 8 2006ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ ዉስጥ ዕድሜያቸዉ ለትምሕርት የደረሰ ከሰወስት ሚሊዮን የሚበልጡ ልጆች የመማር ዕድል እንደማያገኙ ወይም ትምሕርት ጀምረዉ እንደሚያቋርጡ የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) አስታወቀ።ዩኒሴፍ ሰሞኑን አዲስ አበባ ዉስጥ ይፋ ባደረገዉ ጥናት መሠረት ኢትዮጵያ በተለይ በትምሕርት መስክ የዓለም አቀፉን ድርጅት የዓመ-አት ግብ ገቢር በማድረግ ረገድ የተሻለች ብትሆንም የመማር ዕድል የማያገኙት ኢትዮጵያዉን ልጆች ቁጥር ግን ከፍተኛ ነዉ።በጥናቱ መሠረት የመማር ዕድል ካላገኙት ወይም ትምሕርት ከሚያቋርጡት ልጆች ግማሽ ያሕሉ በኦሮሚያ መስተዳድር የሚኖሩ ናቸዉ።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርግስ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ