የልጅነት ልምሻን የማጥፋት ዘመቻ
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 20 2005ማስታወቂያ
ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት ኢትዮጵያ ዉስጥ በሽታዉ አልታየም የዘመቻ ክትባቱም የፖቀጥሏል። የልጅነት ልምሻ ማለትም ፖሊዮን የማጥፋት መርሃግብር ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት ሲቋቋም በወቅቱ ይህ በሽታ በዓመት ከ350 ሺህ በላይ ሰዎችን አካል ያሽመደምድ ነበር። መርሃግብሩ ተነድፎ ዘመቻዉ ተጠናክሮ ይህን የአካል ጉዳት የሚያስከትለዉን በሽታ ለመከላከል የሚያስችለዉ ክትባት በመሰጠቱ ዛሬ ከአፍሪቃ እና እስያ በቀር በቀሪዉ ክፍል ዓለም ታሪክ መሆኑ ነዉ የሚነገረዉ።
በተጠቀሱት ክፍለ ዓለሞችም ቢሆን ከችግሩ ያልተላቀቁት ብዙ የሚባሉ አይደሉም፤ አፍሪቃ ዉስጥ ናይጀሪያ፤ እስያ ደግሞ ፓኪስታንና አፍጋኒስታን። በጤና ዘርፍ ምርምር የሚያካሂዱ ባለሙያዎች አጋጣሚዉ ይህንንም በሽታ እንደፈንጣጣ ሁሉ ታሪክ የሚሆንበት ጊዜ መቃረቡን ያመላክታል እያሉ ነዉ። በያዝነዉ የአዉሮጳዉያን ዓመት ናይጀሪያ ዉስጥ በስድስት ወራት 171 ሰዎች ላይ ብቻ ነዉ በሽታዉ የታየዉ። ከተጠቀሰዉ ቁጥር አብዛኛዉ ታማሚ ደግሞ የተገኘዉ ሙስና፤ አለመረጋጋት በተስፋፋበትና የበሽታዉ መከላከያ ክትባት በአግባቡ ባልተዳረሰባቸዉ የሰሜን ናይጀሪያ ግዛቶች ነዉ። ሁኔታዉ የአካባቢዉን ባለስልጣናት አሳስቧል።
ሸዋዬ ለገሠ
ሂሩት መለሰ