1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ ጉብኝት 

ሐሙስ፣ ጥር 11 2009

ሚኒስትሯ በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፣ ከአፍሪቃ ኅብረት ኮሚሽን ባለሥልጣናት እና ከአሜሪካን ኤምባሲ ሠራተኞች ጋር ይወያያሉ። ሆኖም ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ከዚህ ያለፈ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

https://p.dw.com/p/2W3pB
USA-Afrika-Gipfel 2014
ምስል DW/S. Broll

M M T/ Beri.Wash.( Linda Thomas-Greenfield in Ethiopia) - MP3-Stereo

በዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሊንዳ ቶማስ ግሬን ፊልድ ዛሬ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል ። ከዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተሠራጨው መረጃ መሠረት ሚኒስትሯ በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፣ ከአፍሪቃ ኅብረት ኮሚሽን ባለሥልጣናት እና ከአሜሪካን ኤምባሲ ሠራተኞች ጋር ይወያያሉ። ሆኖም ከዚህ የዘለለ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ዶቼ ቬለ የጠየቃቸው ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የሥራ ኃላፊ ስለ ሚኒስትሯ ጉብኝት መረጃ እንደሌላቸው አስታውቀዋል። አንድ የአካባቢው የጂኦ ፖለቲካ ምሁር ግን ሚኒስትሯ ኢትዮጵያን የሚጎበኙት በኢትዮጵያ የረገበ የመሰለው አመጽ አሜሪካንን በእጅጉ ስለሚያሳስባት ነው ይላሉ። የዋሽንግተን ዲሲው ወኪላችን ዝርዝር ዘገባ አለው። 


መክብብ ሸዋ 


ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ