1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሊቢያ አገናኝ ቡድን ጉባኤ

ዓርብ፣ ሐምሌ 8 2003

ኢስታንቡል ቱርክ ውስጥ ዛሬ የተካሄደው የሊቢያ አገናኝ ቡድን ጉባኤ ኮሎኔል ሞአመር ጋዳፊ ከሥልጣን እንዲወርዱ እንደገና ጥሪ አቀረበ ።

https://p.dw.com/p/Ra6g
ምስል dapd

በጉባኤው ላይ የተሳተፉት ኃያላኑ መንግሥታት ደግሞ የሊቢያውን መሪ የኮሎኔል ሞአመር ጋዳፊን ኃይሎች ለሚወጉት አማፅያን እውቅና ሰጥተዋል ። ከሰላሳ አገራት የተውጣጡ የኃያላኑ መንግሥታት ና ተሰሚነት ያላቸው የአካባቢው አገራት ተወካዮች የተሳተፉበት ይኽው ጉባኤ ጋዳፊን ከሥልጣን ለማውረድ የሚደረገውን ወታደራዊውን ጫና ለማጠናከርም ተስማምቷል ። ጉባኤው ሊቢያ ወደ ዲሞክራሲ እንድትሸጋገር ያስችላታል ያለውን የሰላም እቅድም አውጥቷል ። በሰላም እቅዱ ውስጥ የተባበሩት መንግሥታት እና የአፍሪቃ ህብረት የሚቆጣጠሩት የተኩስ አቁም ተካቷል ። የጎሳ መሪዎችን እና በአሁኑ ሰዓት በጋዳፊ ቁጥጥር ስር ካለችው የትሪፖሊ ከተማ የተውጣጡ ተወካዮችን የሚያሳትፍ ብሔራዊ ጉባኤ የማካሄድ ሃሳብም ቀርቧል ። ከጉባኤው በመቀጠል በሃገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለማስፈን ህገ መንግሥት ማርቀቅና የምክር ቤት ምርጫዎችን ማድረግ እንደሚገባም ተጠቁሟል ። የጂዳው ወኪላችን ነብዩ ሲራክ ስለ ጉባኤው ሂደት ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል

ነብዩ ሲራክ

ሂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ