1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሄይቲ መልሶ ግንባታ

ረቡዕ፣ የካቲት 17 2002

በጥር ወር መጀመሪያ አካባቢ የደረሰዉ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ የሄይቲን ዋና መዲና ፓርት ኦ ፕራንስን ክፉኛ ጎድቷል።

https://p.dw.com/p/MAAM
ምስል Tihomir Streklj
ተደጋግሞ የታየዉ የመሬት ነዉጥ ካጠፋዉ ህይወት በተጨማሪ ተናግተዉ ሳይፈርሱ የቀሩትም ህንፃዎች ሳይቀር ሲያፈርስ ሲደረማምስ ታይቷል። በዚህ አደጋ የአገሪቱን ታሪክ የሚገልፁ ባህላዊ ቅርሶች ሳይቀሩ እንዳልነበሩ ሆነዋል። ነዉጡ የሰዉ ህይወት ከማጥፋቱና ንብረት ከማዉደሙ ባሻገር የቀሪዎቹን መንፈስ አስጨንቋል። ያም ሆኖ ከመልሶ ግንባታዉ ጥረት በተጓዳኝ መንፈሳዊዉና ባህል አንፀባራቂ ተግባራት የወደመችዉን ከተማ ጨርሳ እንዳት ጨልም ረድተዋል። የዶቼ ቬለዉ ማርቲን ፕላንስኪ ሁኔታዉን ቃኝቶ ከፖርት ኦ ፕራንስ ለላከዉ ዘገባ ሸዋዬ ለገሠ። ማርቲን ፕላንስኪ ፣ ሸዋዬ ለገሠ ሂሩት መለሰ