1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሂዩማን ራይትስ ዎች ዓመታዊ ዘገባ

ማክሰኞ፣ ጥር 13 2006

ሂዩማን ራይትስ ዎች የተሰኘው ዓለም ዓቀፋዊ የሰብዓዊ መብት ተንከባካቢ ተቐም በዛሬው ዕለት ባወጣው ዓመታዊ ዘገባ በዓለም ላይ የ90 ኣገሮችን የሰብዓዊ መብት ይዞታ ገምግሟል።

https://p.dw.com/p/1AuTA
Untersuchungen in den russischen Nichtregierungsorganisationen Human Rights Watch
ምስል picture-alliance/dpa

መቀመጫውን ኒዮርክ-ዩናይትድ ስቴትስ ያደረገው ሂዩማን ራይትስ ዎች እንደሚለው በዚህ ዓመት ይበልጥ ጎልቶ የታየው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ጦርነት በሚካሄድባቸው አካባቢዎች የተከሰቱ የመብት ጥሰቶች ናቸው። እነዚህም የሰላማዊ ሰዎች ግድያን ጨምሮ ዘረፋና ስደት የመሳሰሉ ጥቃቶችን እንደሚያጠቃልል ሪፖርቱ ኣመልክቷል።

በሂዩማን ራይትስ ዎች የኣፍሪካ ክፍል ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዳንዔል በቀለ እንደሚዘረዝሩት የኢትዮጵያ መንግስትም የጸረ ሽብር እና የሲቪክ ማህበራት ህግጋትን ጨምሮ በበርካታ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ተከሷል።

በተለይም የኤርትራ መንግስት ደግሞ ለዓለም ህብረተሰብ በሩን ከመዝጋት ኣንስቶ ያለፍርድ ቤት መታሰር እና ሌሎች በርካታ ሰቆቃዎችን በመፈጸም እጅግ የተበላሸ ሪኮርድ ተሰቶታል ተብሏል።

ጃፈር ዓሊ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ