የሁለቱ ሱዳኖች መሪዎች ድርድር
ረቡዕ፣ መስከረም 16 2005ማስታወቂያ
የሰሜንና የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንቶች አዲስ አበባ ዉስጥ የሚያደርጉት ድርድር ወደ አግባቢ ዉጤት መቃረቡ ተነገረ።የድርድሩን ሒደት የሚከታተሉ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች እንዳስታወቁት የሁለቱ ሐገራት መሪዎች አብዛኛ ልዩነታቸዉን አስወግደዋል።ሁለቱ ሱዳኖች የድንበር ግዛት ይገባኛል፥ የነዳጅ ዘይት ሐብት ክፍፍል፥ አንዱ የሌላዉን ተቃዋሚ የመደገፍና የዜግነት ጉዳይ ጠብ- ልዩነታቸዉን በሰላም ለማስወገድ የሁለቱ ሐገራት ዲፕሎማቶችና ባለሥልጣናት በተከታታይ ሲደራደሩ ነበር።ካለፈዉ ዕሁድ ጀምሮ ደግሞ ፕሬዝዳት ዑመር ሐሰን አል-በሽርና ፕሬዝዳት ሳልቫኪር ራሳቸዉ አዲስ አበባ ዉስጥ እየተደራደሩ ነዉ።የኢትዮጵያ የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ቀትር ላይ እንዳስታወቁት በመሪዎቹ መሐል ልዩነት ቢኖርም መስማማታቸዉ አይቀርም።
ስምና ዜግነታቸዉ እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ ዲፕሎማት እንዳስታወቁት ደግሞ መሪዎቹ ከመጨረሻዉ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።ሮይተር ዜና አገልግሎት የድርድሩን ሒደት በቅርብ ያዉቃሉ ያላቸዉ ዲፕሎማት እንዳሉት ስምምነቱ ፊርማ ብቻ ነዉ የቀረዉ።የሁለቱ ሱዳኖች ባለሥልጣናትም ሆኑ አደራዳሪዎች ግን ሥለ ድርድሩ ዉጤት እስካሁን በጋራም ሆነ በተናጥል የሰጡት መግለጫ የለም።
ሂደቱን በመከታተል ላይ የሚገኘው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ስለ ሁለቱ ሱዳኖች ድርድር የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይንና አንድ የፖለቲካ ተንታኝ አነጋግሮ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ሂሩት መለሰ
ሸዋዮ ለገሰ