ዓ/አቀፍ የወባ መከላከያ ቀን በኢትዮጵያ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 18 2004ማስታወቂያ
መንግሥታትና አለም አቀፍ ድርጅቶች የወባ በሽታን ለመካለል የሚያወጡት ገንዘብ ባለፉት አስር ዓመታት ብዙ ጨምሯል።የዓለም ጤና ድርጅት የበላይ ማርጋሬት ቻን ትናንት እንዳስታወቁት ባለፉት ዓመታት ወባን ለመከለክልና በሽተኞችን ለማከም ተጨማሪ ገንዘብ በመዉጣቱና ልዩ ትኩረት በመሠጠቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ከሞት ተርፈዋል።ይሁንና ሐላፊዋ አክለዉ እንዳሉት ወባ አሁንም ከዓለም በርካታ ሕዝብ ከሚገድሉ አምስት በሽታዎች አንዱ ነዉ። በዚሕም ሰበብ የዘንድሮዉ የፀረ-ወባ ቀን አብይ መርሕ በጣሙን የአፍሪቃ ሕፃናትን የሚፈጀዉን በሽታ ለመከላከል የሚደረገዉ ጥረት እንዲጠናከር የሚጠይቅ ነዉ።በኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚንስቴር የወባ መከላከያ ዘርፍ አስተባባሪ ወይዘሪት ሕይወት ሰለሞን እንዳስታወቁት የፀረ-ወባ ዕለት ኢትዮጵያ ዉስጥም ተከብሮ ነዉ የዋለዉ።
የወባ በሽታ መቀነሱ ቢነገርም ባለፈዉ የጎሮጎሮሳዉያኑ አመት ብቻ ከስድስት መቶ ሐምሳ ሺሕ በላይ ሕዝብ በትንሽ ወጪ በሚገዛዉ መድሐኒት እጦት በወባ በሽታ ሞቷል።ከከሟቾቹ ከአምስት መቶ ሥልሳ ሺሕ የሚበልጡት ጨቅላ ሕፃናት ነበሩ።ከሟቾቹ ከዘጠና ከመቶ የሚበልጡት ደግሞ አፍሪቃዉያን ነበሩ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ
አርያም ተክሌ