ዓለም አቀፉ የኤድስ ጉባዔ በደርባን
ሰኞ፣ ሐምሌ 11 2008ማስታወቂያ
« ፀረ «ኤች አይ ቪ» መድሐኒትን ለሁሉም በእኩል ማዳረስ» የሚል መርህ እንደያዘ የተገለፀዉ ይህ ጉባዔ እስከ ፊታችን ዓርብ ድረስ ይዘልቃል። የደቡብ አፍሪቃ የቀድሞ ፕሬዚደንትና የነጻነት አርበኛ ኔልሰን ማንዴላ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ በዓለማችን ከታዩት እጅግ አስከፊ ከሚባሉት ስጋቶች አንዱ ነው ባሉት በኤድስ ላይ ጠንካራ ርምጃ እንዲወስድ ካሳሰቡ ከ16 ዓመታት በኋላ ደርባን ይህን መሰል ጉባዔ ስታካሂድ አሁን ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ጆሃንስበር የሚገኘዉ ወኪላችን መላኩ አየለን ስለጉባዔዉ አጀማመር እንዲሁም ደቡብ አፍሪቃ «ኤች አይ ቪ» ን ለመዋጋት እያደረገችዉ ስላለዉ ጥረት ጠይቀነዉ ነበር።
መላኩ አየለ
አዜብ ታደሰ
ሸዋዬ ለገሠ