ወግ አጥባቂዎቹ አስተማማኝ ድምፅ አግኝተዋል
እሑድ፣ መስከረም 17 2002ማስታወቂያ
በጀርመን አቆጣጠር እኩለ ሌሊት ግድም ይፋ በሆነዉ ዉጤት መሠረት፥ ወግ አጥባቂዉ የአንጌላ ሜርክል እሕትማማች ፓርቲ CDU/CSU ካጠቃላዩ የምክር ቤት መቀመጫ 238ቱን በማሸነፍ-የአንደኝነቱን ሥፍራ ይዟል።ሽታይማየር የሚወክሉት የሶሻል ዲሞክራቶቹ ፓርቲ SPD መጀመሪያ ከተገመተዉም ቁልቁል ወርዶ 148 መቀመጫዎች አግኝቷል።የነፃ ዲሞክራቶቹ ፓርቲ FDP 93 መቀመጫዎችን አግኝቷል።የግራዎቹ ፓርቲ 76 አረንጓዴዎቹ ደግሞ 67 መቀመጫዎችን አሸንፈዋል።
ነጋሽ መሐመድ
ነጋሽ መሐመድ