ወይዘሪት ብርቱኳን ሚዴቅሳ እንዲፈቱ በቲዩቢንገን የተዘጋጀ የሩጫ ውድድር
ዓርብ፣ መስከረም 7 2003ማስታወቂያ
የኢትዮጵያው ታቃዋሚ ፓርቲ የአንድነት ለፍትህና ዲሞክራሲ ፓርቲ መሪ ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከእስር እንደለቀቁ እዚህ ጀርመን የሚንቀሳቀስ የኢትዮጵያውያን የመብት ተሟጋች ድርጅት ና ሁለት የጀርመን ባለስልጣናት ጠየቁ ። በጀርመን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ፣ በጀርመን ምክር ቤት የአረንጓዴዎቹ ፓርቲ እንደራሴ እና የቱቢንገን ከተማ አስተዳደር አባል በየፊናቸው እንዳሉት ወይዘሪት ቡርቱኳን የታሰሩት በፓለቲካ አቋማቸው እንጂ ሌላ ወንጀል ፈፅመው አይደለም ። ወይዘሪት ቡርቱካን እንዲፈቱ ግፊት ለማድረግ የፊታችን ዕሁድ ቱቢንገን ውስጥ የሩጫ ውድድር ይደረጋል ። መሳይ መኮንን
መሳይ መኮንን
ነጋሽ መሐመድ