ወቅትን ጠብቀዉ የሚከናወኑ ልምዶች
ሐሙስ፣ ግንቦት 23 2004ማስታወቂያ
በአገራችን የበዓላት አከባበር እንደ አካባዊዉ ባህልና እና እንደ የልማዱ ይለያያል። የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች አገረሰባዊዉ ልማድም የተለያየ ፍች ይሰጠዋል።
በግንቦት ወር ንፍሮ መቀቀል እና እደጅ ተሰብስቦ በጋራ መብላት ወቅትን ጠብቀዉ ከሚከናወኑ ልምዶች አንዱ ነዉ። ባህላችን ከሃይማኖታችን ሃዕማኖታችን ከባህላችን የተያያዘ ነዉ ያሉን እና የቤተ ክህነት ጉዳዮች አዋቂና በነዚሁ ጉዳዮች ላይ ልዩ ልዩ ጥናታዊ ጽሁፎችን ያዘጋጁት መላከ ምክር ከፍ ያለዉ መራኒ በአሉ ሲሉ ሰፋ ያለ ማብራርያ ሰጥተዉናል። በአገራችን በሚገኝ በተለያየ ህብረተሰብ ዘንድ የተለያየ እምነት እና ባህል በአላት ይከበራሉ ሲሉ የገለጹልት በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የቋንቋዎች እና ባህሎች አካዳሚ የስራ ሃላፊ የሆኑት ዶክተር ባይለየኝ ጣሰዉ ፣ይህ አይነቱ ቱፊት ሊጠና ሊታወቅ ይገባዋል ባይ ናቸዉ ቆየት ባለዉ እምነትም በማለት መረጃ ሰጥተዉናል። የለቱ የባህል መድረክ ወቅትን ጠብቀዉ ከሚከናወኑ ልምዶች መካከል ጥቂቶቹን ያስቃኘናል። ሙሉዉን መሰናዶ ያድምጡ!
አዜብ ታደሰ
ሂሩት መለሰ