ወሲባዊ ጥቃት በኢትዮጵያ
እሑድ፣ ኅዳር 21 2007ማስታወቂያ
የ10ኛ ክፍል ተማሪ እና የ17 ዓመት ታዳጊ ነበረች። አዲስ አበባ ውስጥ ከአየር ጤና ወደ ጦር ኃይሎች ልትጓዝ በተሳፈረችበት ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ በነበሩ አምስት ሰዎች ታፍና ተወስዳ በተደጋጋሚ በመደፈሯ ለሞት የተዳረገችው-ሐና ላላንጎ። ታዳጊዋን አፍነው በመውሰድ ደፍረዋል በሚል የተጠረጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው በምርመራ ላይ ናቸው። በሐና ላላንጎ ላይ የተፈጸመው ወሲባዊ ጥቃት በመገናኛ ብዙሃን ይፋ ከሆነ በኋላ በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል።
ፌስቡክን በመሳሰሉ ማህበራዊ ድረ ገጾች ኢትዮጵያያን ፎቶ ግራፏን በመለጠፍ እና 'ፍትህ ለ ሐና' የሚሉ ሃሳቦችን በማስተጋባት ቁጣቸውን ገልጸዋል።በዚህ ሳምንት የዶይቸ ቬለ የውይይት መድረክ ወሲባዊ ጥቃት በኢትዮጵያ ያለውን ገጽታ እንፈትሻለን።
እሸቴ በቀለ
ልደት አበበ