1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከፊሉ የምርጫ ውጤት እና የመድረክ አስተያየት

ሐሙስ፣ ግንቦት 20 2007

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ባለፈው እሁድ የተደረገውን ሀገራዊ ምርጫ ከፊል ውጤት፣ የምርጫው ሂደት ሰላማዊ አልነበረም በሚል አለመቀበሉን ገለጸ።

https://p.dw.com/p/1FXj4
Wahlplakate vor der Parlamentswahl in Äthiopien am 23.Mai
ምስል DW

[No title]

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአራት ቀናት በፊት በተካሄደው ሀገራዊ ምርጫ እስካሁን ከክልሎች በደረሰው ከፊል ውጤት ገዢዉ ፓርቲ ኢ ህ አ ዴ ግ እና አጋር ድርጅቶች ለሕዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤቶች አብላጫዉን ድምፅ ማግኘታቸዉን በትናንቱ ዕለት መግለጹ ይታወቃል። በቦርዱ መግለጫ መሠረት፣ ኢ ህ አ ዴ ግ እና አጋር ድርጅቶች ከ547 የምክር ቤቶች መንበሮች 442 አግኝተዋል። የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ፣ በምህፃሩ መድረክ ይህንኑ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያወጣውን ከፊል ውጤት፣ የምርጫው ሂደት ሰላማዊ አልነበረም በማለት እንደማይቀበለው ለዶይቸ ቬለ ገልጾዋል።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ