ከደም አፋሳሹ ግጭት በኋላ በካይሮ የተጠራዉ አስቸኳይ ስብሰባ
እሑድ፣ ሚያዝያ 30 2003ማስታወቂያ
በካይሮ በአንድ ቤተክርስትያን ቅጽር ግቢ በሙስሊም እና በኮፕት ክርስትያኖች መካከል በተነሳ ግጭት አስር ሰዎች ሞተዋል፣ ከመቶ በላይ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል። ግጭቱ የተቀሰቀሰዉ በመቶ የሚቆጠሩ ሙስሊሞች እስልምና ሃይማኖትን የተቀበለች የክርስትና እምነት ተከታይ በቤተክርስትያን ታግታለች ብለዉ በማመን ወደ ቤተክርስትያን ዘልቀዉ ከገቡ በኳላ ነበር። እንደ ግብጹ የቴሌቭዝን ዘገባ ሁለቱ የሃይማኖት ቡድኖች በግጭቱ ተወርዋሪ እና እሳት አመንጭ መሳርያን መጠቀማቸዉ ተጠቅሶአል።
አዜብ ታደሰ
መስፍን መኮንን