እጅግ ግዙፉ የራዲዮ ቴሌስኮፕ ጣቢያ(SKA)
ረቡዕ፣ ግንቦት 15 2004የሚያስችለው ቴሊስኮፕ ደቡብ አፍሪቃ እንዲተከል ፤ የዓለም አቀፍ ባንኮችና ኩባንያዎች ማኅበር ሊወስን ይችላል የሚል ግምት ያላቸው በርካታ ናቸው። የውሳኔው መዘግየት የሆነው ሆኖ ሁለቱንም ተፎካካሪዎች ትዕግሥት እያሳጣ ነው። ደቡብ አፍሪቃ ቢቀናት ለእርሷም ሆነ ለመላው አፍሪቃ ምን ፋይዳ ያስገኝ ይሆን? በሳይንስና ኅብረተሰብ ቅንብራችን ተከታተሉት።
Square Kilometre Array(SKA) የተባለው፣ 2 ቢሊዮን ዩውሮ ወጪ የሚጠይቀው ፕሮጀክት አቅድ የወጣው ከ 21 ዓመት በፊት ነው። እ ጎ አ ከ 2004 ዓ ም አንስቶ ሥራውን በተሟላ ሁኔታ እንደሚጀምር የሚጠበቀው ፕሮጀክት አንድ ሺ ያህል የኤሌክትሮኒክስ ጆሮዎች የሚተከሉበት ሲሆን፣ ከቅርብም ሆነ ከሩቅየኅዋ የኅዋ ክፍል ማንኛውንም የራዲዮ ሞገድ የሚስብ ነው። ጉልበቱም የአንድ መቶ ሚሊዮን ኮምፒዩተሮች ሞተርን የሚያጠቃልል ነው።
ይኸው በዓለም ውስጥ እጅግ ግዙፍ የራዲዮ ቴሌስኮፕ(SKA)ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ቢተከል ለራሷ ለደቡብ ብሎም ለቀሪው የአፍሪቃ ክፍለ-ዓለም የሚሰጠው ጥቅም እንዴት ይገመገማል? በፕሪቶሪያ የአስዋኔ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ሁለት ፕሮፌሰሮችን አነጋግሬ ነበር ፤ በቅድሚያ በዚያ ዩኒቨርስቲ፤ በፈጠራ ምርምር ረገድ፤ የኤኮኖሚ ክፍል ዋና ስራ አስኪያጅ ፕሮፌሰር ራሲጃን ማሃራጅ፣ ፕሮጀክቱ እንዲጀመር ለመወሰን ጊዜ መውሰዱ፣ ስላስከተለው ሁኔታ እንዲህ ሲሉ በማብራራት ይጀምራሉ።
በዚያው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ሌላው፣ ኢትዮጵያዊው ፕሮፌሰር ዶ/ር ማሞ ሙጨ፣ እንዲህ ነበረ ያሉን።
ይኸው ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ፤ ከ SKA አኳያ ማን ዓይነት ድርሻ ማበርክት ይችል ይሆን?
ተክሌ የኋላ
ሒሩት መለሰ