ኢትዮጵያ፤ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች ይዞታ10 መጋቢት 2006ረቡዕ፣ መጋቢት 10 2006በጋምቤላ የሚኖሩ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች የዓለም ዓቀፋ ኅብረተሰብ አስፈላጊዉ ድጋፍ ካላደረገላቸዉ በቀር በረሃብና በሽታ ምክንያት ለአደጋ ሊጋለጡ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች አስተዳደር አስጠነቀቀ።https://p.dw.com/p/1BSRgምስል DW/Y. Gebreegziabherማስታወቂያ ተቀማጭነታችዉ አዲስ አበባ የሆነ የአስር ሃገራት አምባሳደሮች ትናንት በጋምቤላ የስደተኞቹን መጠለያ ጎብኝተዋል። በተጨማሪም በድንበር አካባቢ ያለዉን የስደተኞች ጎርፍ በቦታዉ ተዘዋዉረዉ መመልከታቸዉንም በስፍራዉ የተገኘዉ ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር በላከዉ ዘገባ አመልክቷል። ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር ሸዋዬ ለገሠ አርያም ተክሌ