ኢትዮጵያ የሥልክና የኢንተርኔት ችግር
ሐሙስ፣ ሐምሌ 24 2006ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን የሚሠጠዉ የሥልክና የኢንተርኔት አገልግሎት እጅግ ደከማ።በየጊዜዉ የሚቆራረጥና አንዳዴም ጨርሶ የሚጠፋ ወይም የሚቆረጥr በመሆኑ ተገልጋዩ ሕዝብ የዐለት ከዕለት እንቅስቃሴ በተለይ ግንኙነቱ መታወኩን በየጊዜዉ እየገለጠ ነዉ።የሐገሪቱን የሥልክና የኢንተርኔት አግልግሎት በብቸኝነት የሚቆጣጠረዉ ኢትዮ-ቴሌኮም በየጊዜዉ ለሚነሱት ወቀሳዎችና ለሚፈጠሩት ችግሮች ምክንያት የሚላቸዉን ቴክኒካዊ ሠበቦች መደርደሩ አልቀረም።ችግሩ ግን የመቃለል እዝማሚያ አልታየበትም።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሐይለጊዮርጊስ እንደሚለዉ ባለፉት ጥቂት ወራት ደግሞ ከወትሮዉም የከፋ ነዉ።ኢትዮ ቴሌኮም አሁንም አዲስ ምክንያት ስጥቷል።ምክንያቱን አብረን እንስማ።
ጌታቸዉ ተድላ ሐይለጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ