ኢትዮጵያ እና ምርጫ 2007
እሑድ፣ ግንቦት 16 2007ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስታወቀዉ መሠረት ዛሬ ዕሁድ የሚደረገዉን ምርጫ አጠቃላይ ዉጤት ይፋ ለማድረግ ከድምፅ መስጪያዉ ዕለት በኋላ አንድ ወር ያሕል ጊዜ ይወስዳል።ይሁንና የምርጫ ጣቢያዎች የየአካባቢያቸዉን ምርጫ ዉጤት በየአካባቢያቸዉ ማሳወቅ እንደሚችሉ ተመልክቶአል። በአዲስ አበባ በሆሳዕና እና በአምቦ የሚገኙ ዘጋቢዎቻችን የተመለከቱዋቸዉን በፎቶና በድምፅ እየዘገቡ ናቸዉ።
ዶቸ ቬለ የአማርኛ አገልግሎት የድምፅ አሰጣጡን ሒደት በቀጥታ ይከታተላል።እዚያዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከሚገኙ ዘጋቢዎቻችን፤ ከዚሕ ከቦንና ከሌሎችም አካባቢዎች የምናጠናቅራቸዉን ዘገቦች ከራዲዮ ሥርጭታችን በተጨማሪ በድረ ገጻችን ፣ www.dw.de/amharic ላይ (Live-Blog)መከታተል ትችላላችሁ። በፌስ ቡክ ገፃችንም ሥለምርጫዉና ከምርጫዉ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በሚመለከት ከድምፅ መስጫዉ ዕለት ጧት ጀምራችሁ እስኪጠናቀቅ ድረስ እርስ በርስና ከኛ ጋር ተወያዩ።በድምፅ መስጪያዉ ዕለት ያነሳችሁትን ፎቶ ግራፍ፤ በፌስ ቡክ ገፃችን፤ ትዝብታችሁን ደግሞ በSMS ላኩልን።የSMS መቀበያ ቁጥራችን 0049 172 26 66 944 ነዉ።ሥልክ መደወል ከቻላችሁም በ0049 228 429 164 995 መልዕክት ብትተዉሉን ይደርሰናል።እናሰራጨዋለንም።የድምፅ አሰጣጡ ሒደት «ተዛብቷል» ብላችሁ ካመነችሁ አስተያየታችሁን ብትልኩልን የሚመለከተዉን ወገን አነጋግረን መልስ ለማግኘት እንሞክራለን። መልካም ምርጫ።
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ