ኢትዮጵያ በዘመነ ኢሕአዴግ
እሑድ፣ ግንቦት 21 2008ማስታወቂያ
ኢትዮጵያን ለ17 ዓመታት የመራዉ የደርግ ሥርዓት በሐይል ከሥልጣን የተወገደበት፤ የቀድሞዉ አማፂ ቡድን የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) ሥልጣን የያዘበት ሃያ አምስተኛ ዓመት ወይም የብር ኢዮቤልዩ በዓል በተለያየ ድግሥእየተከበረ ነዉ። በዛሬዉ ዉይይታችን የኢትዮጵያን የ25 ዓመት ጉዞ በወፍ በረር እንቃኛልን። ወይይታችን በተለይ ሠላምን በማስፈን፤ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን በማስረፅ እና ምጣኔ ሐብታዊ እድገትን በማጠናከሩ ረገድ የተደረገዉ ጥረት፤ ዉጤቱና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያለዉን ፋይዳ ባጭሩ ይቃኛል።
ነጋሽ መሐመድ