ኢትዮጵያዊነት ሥነ-ምግባር እስከምን?
ቅዳሜ፣ ሰኔ 15 2005ማስታወቂያ
ማኅበረሰባችን ክብርን ድጋፉ ያደረገ ሃይማኖታዊ አሻራ የሰፈረበትና የታነጸ ባሕል ያለው ነው፡፡ግን ኢትዮጵያዊ ግብረገብነት እና ጨዋነት ክብንርን የመጠበቅ ባህላችን እምን ደረጃ ላይ ይገኛል? በሌላ በኩል እዉነታዉ የሚደገፍ ባይሆንም እህት ወንድሞቻችን ላይ የሞራል ዉድቀት እንዳይደርስ ባህላችን እንዳይሸረሸር በበኩላችን ምን እያደረግን ነዉ? መገናኛ ብዙሃን፤ የትምህርት ቀቋማትና፤ የትምህርት ሥርዓታችን፤ ጠቃሚ ባህላዊ እሴቶችንን በቅርስነት እንድናቆይ ቢያስተምሩ ወጣቱ በሥነ ምግባር ታንጾ ሀገር ገንቢ ለዓለምም ጠቃሚ ዜጋ እንደሚሆን አያጠያይቅም። ስህተቶችን በመነጋገር እና በመተራረም የመፍታት ባህሪያችንን እናጎልበት ያሉንን የአራት ባለሞያዎች ሙሉ ቃለ ምልልስን፤ ከዘገባዉ ስር ያለዉን የድምፅ ማሳያ ቁልፍ በመጫን ያድምጡ።
አዜብ ታደሰ