1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮዽያዊው የእግር ኳስ ታላቅ ሰው አረፈ

ዓርብ፣ ታኅሣሥ 8 2003

የ70ዓመት የዚህች ዓለም ቆይታውን ትላንት ፈጸመ። ታላቁ ኢትዮዽያዊ የእግር ኳስ ሰው- መንግስቱ ወርቁ።

https://p.dw.com/p/Qelh
ምስል Isna

ሶስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮዽያ እንድታገኝ ያደረገ፤ ለብሄራዊ ቡድን በተሰለፈባቸው 96ግጥሚያዎች በአጠቃላይ 61 ግቦችን ከመረብ ያገናኘ፤ የእግር ኳስ ድንቅ ቴክኒሺያን ነበር መንግስቱ ወርቁ። ቁመቱ አጭር ቢሆንም ከሁለት ሜትር በላይ በመዝለል በጭንቅላቱ ኳስዋን ገጭቶ ጎል የማስቆጠር ብቃቱን ያዩት አሁን ድረስ በአድናቆት ይናገሩለታል። ዛሬ በአዲስ አበባ የቀብር ስነ ስርዓቱ እንደተፈፀመ የአዲስ አበባው ወኪላችን ታደሰ እንግዳው ዘግቧል።

ታደሰ እንግዳው

መሳይ መኮንን
ሂሩት መለሰ