አፍሪቃውያን ስደተኞች በእስራኤል
ረቡዕ፣ ኅዳር 23 2002ማስታወቂያ
ለዶይቼቬለ የአማርኛ ክፍል አስተያየታቸውን የሰጡት ኤርትራውያንና ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች እንደሚሉት በሀገሪቱ ረዥም ዓመታት የቆዩ ጥገኝነት ጠያቂዎች አንደ አዲስ አመልካች እንዲመዘገቡ እየተደረገ ሲሆን የሚሰጣቸው የስራ ፈቃድ የጊዜ ገደብም ከቀድሞው ዝቅ ብሏል ። አንዳንዶቹም ወደ ግብፅ የመባረር ስጋት ላይ ናቸው ። የእስራኤል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህገ ወጥ የተባሉትን እነዚህን ስደተኞች ወደ ግብፅ መመለስ አለመመለስ ለመወሰን ጉዳዩን እየተመለከተ ነው ።
ዜናነህ መኮንን ፣ ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ