«አገር ፍቅር ከእናቴ ቤት በላይ የኖርኩበት ነዉ» አብራር አብዶ
ሐሙስ፣ ጳጉሜን 5 2007ማስታወቂያ
«የኢትዮጵያ ብሔራዊ ኪነ-ጥበብ ማዕከል» ለኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጉዋል ሲል የሸለመዉን አንጋፋዉን አርቲስት አብራር አብዶን ፔጥሮስ ያችን ሰዓት የተሰኘዉን ድራማ በመድረክ ላይ አቅርቦ ተመልካችን አስደምሞአል። ቅዳሜ ነሐሴ 30/ 2007 ዓ,ም ፍርናክፈርት ካልክ ሃይም በሚገኝ ሰፊ አደራሽ ዉስጥ በተከናወነዉ የክብር ሽልማት አሰጣጥ ሥነ-ስርዓት በኢትዮጵያና አዉሮጳ ነዋሪ የሆኑ በርካታ አርቲስቶችም ተገኝተዉ ነበር። የባህል መድረካችን የኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ማዕከል ጀርመን ፍራንክ ፈርት ላይ ያዘጋጀዉን መሰናዶ ያስቃኘናል ።