«አዳብና» ለመስቀል
ሐሙስ፣ መስከረም 15 2007ማስታወቂያ
1600 እድሜን እንዳስቆጠረ የሚነገርለትና፤ በተለያዩ ቱፊቶች እና ቀለሞች የደመቀዉ የኢትዮጵያዉ የመስቀል በዓል አከባበር፤ በተባበሩት መንግስታት የሳይንስ የትምህርትና ባህል ማዕከል /UNESCO/መዝገብ በዓለም ቅርስነትም መመዝገቡ ይታወቃል። የዕለቱ ዝግጅታችን በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ የአዳብና ክትፎ ቤት ባለሞያዎችን በመስቀል በዓል ስለሚዘጋጀዉ የተለያየ አይነት ክትፎ እና ስለመስቀል አከባበር እንዲያጫዉቱን ጋብዘናል።