አዲስ ዓመት እና እቅዶች
ዓርብ፣ ጳጉሜን 2 2004ማስታወቂያ
ለዛሬ አራት ወጣቶችን መጪውን አመት 2005 ዓ ም አስመልክቶ አዲስ እቅድ በአዲስ አመት ያወጡ እንደው ጠይቀናቸዋል። ወጣት አዲሱ ግርማ ፤ ከ አዲስ አበባ ዮንቨርሲቲ በአካባቢያዊ እና ክፍለ ሀገራዊ ፕሮግራም በዚህ አመት 2ኛ ዲግሪውን አግኝቷል። ያለ እቅድ እንደ ማይንቀሳቀስ ነው የነገረን።ለምን እንደሆነ ገልፆልናል።
ህይወት ይልማ 20 ዓመቷ ነው። እቅድ እስካሁን ኖሮኝ አያውቅም ትላለች፤
ሌላው ወጣት አህመድ ማሕመድ ነው ከጅማ። በከተማ ጥናት ነው የተመረቀው። እሱም እንደ አዲሱ በእቅድ መኖር ወሳኝ ነው ብሎ ያምናል።
በጀርመን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንስ በየትኛው የዘመን አቆጣጠር ነው እቅድ የሚያወጡት?ስንዱ ፀጋዬ በባድ ሆምቡርግ ከተማ ነው የምትኖረው፤ ጨርሶ እቅድ ሳወጣ ቅርብ ጊዜዬ ነው ብላናለች። የኢትዮጵያው አዲስ አመት እቅዷን ለማደስ ጥሩ አጋጣሚ የሆነላት ይመስላል።
ወጣቶቹ ለሰጡንን አስተያየት ማድመጥ ይቻላል።
ልደት አበበ
ተክሌ የኋላ