1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አዲሱ የኢጣልያ ጠ/ሚኒስትር የአዉሮጳ ጉብኝት

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 23 2005

አዲሱ የኢጣልያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤንሪኮ ሌታ የሁለቱን የኢጣልያ ምክር ቤቶች ይሁንታ ጠይቀዉ እጎአ ከ1948 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥምር መንግሥት መስርተዋል። ሌታ የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ስልጣን እንደያዙ ጀርመንን ፈረንሳይን እና የአዉሮጳ ህብረትን በመጎቭኘት ላይ ናቸዉ።

https://p.dw.com/p/18QDs
German Chancellor Angela Merkel and Italian Prime Minister Enrico Letta address news conference at the Chancellery in Berlin, April 30, 2013. REUTERS/Fabrizio Bensch (GERMANY - Tags: POLITICS)
ምስል Reuters

ኤንሪኮ ሌታ ትናንት አመሻሹ ላይ ጀርመን በርሊን ከመራኂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል ተገናኝተዉ በአዉሮጳ ኅብረት ሀገርት ዉስጥ ያለዉን የኢኮኖሚ ቀዉስ በጋራ ትብብር እንሚወጡት ተናግረዉ በተለይ አዉሮጳ ስኬት የሚኖራት የጣልያን እና የጀርመን ግንኙነት ሲጎለብት መሆኑን ተናግረዋል። በቀጣይ ዛሪ ወደ ፈረንሳይ ያቀኑት አዲሱ የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትር ኤንሬኮ ሌታ ሀገራቸዉ ከሚታየዉ ከፍተኛ የሥራ አጥነት፤ ከፍተኛ ዕዳ ቀዉስ እንዲሁም ባጠቃላይ ካለችበት የኢኮኖሚ ድቀት፤ ለመዉጣት ምን ዓይነት የማሻሻያ መረሃ-ግብር ይዘዉ ይሆን? በብራሰልስ የሚገኘዉን ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴን ጠይቄዉ ነበር።

ገበያዉ ንጉሴ
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ