አዲሱ የአዉሮጳ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
ማክሰኞ፣ ጥር 8 2004ማስታወቂያ
ጀርመናዊዉ የአዉሮጳ ሕብረት ምክር ቤት እንደራሴ ማርቲን ሹልስ የምክር ቤቱ ፕሬዝዳት ሆነዉ ተመረጡ።ሹልስ እስካሁን በሕብረቱ ምክር ቤት የሶሻል ዲሞክራት ፓርቲ እንደራሴዎች ተጠሪ ነበሩ።ከእንግዲሕ ላለፉት ሁለት አመታት ተኩል ምክር ቤቱን በፕሬዝዳትነት ከመሩት ፖለንዳዊዉ የቀኝ ዘመም ፓርቲዎች ተወካይ ዠርዚ ቡዜክን ተከትዉ ይሰራሉ።የሹልስ የፕሬዝዳትነት ሥራ ዘመን እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር እስከ 2014 ድረስ ይዘልቃል።የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴ ዝር ዝር ዘገባ አለዉ።
ገበያዉ ንጉሴ
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ