አዲሱን ዘመን ቅበላ በዶቸ-ቬለ
ሐሙስ፣ መስከረም 9 2000ማስታወቂያ
አስራ ሶስት ወር ፀሃይ የሚፈነጥቅባት ኢትዮጽያም የራስዋ የሆነ የቀን ቀመር እንዳላት፣ ዘንድሮ ሁለተኛዉን አማአት በማክበር ላይ መሆንዋን በዉጭ የምንገኝ ኢትዮጽያዉያን አስረድተናል። ጀበናዉን ጥደን ቡናዉን አንከሽክሸን ሲኒዉን ደርድረን እጣኑን አጭሰን፣ የኢትዮጽያን ባህላዊ የቡና አፈላል አሳይተናል። ኢትዮጽያ የቡና መገኛ አገር እንደሆነች ለማያዉቁ ገልጸናል። ስለ ባህላዊ መስተንግዶአችን በሰፊዉ ያድምጡ መልካም ቆይታ