አዝማሪ ከየት ወደ የት
ሐሙስ፣ ጥቅምት 18 2008ማስታወቂያ
«ኧረ እናንተ ሰዎች ከታሪክ ተማሩ፤ እንደ አባቶቻችን ምን እንደነበሩ፤ አዝማሪ ይሉናል አዝማሪ ክሳቸዉ፤ የተበላሸዉን ስላደስልናቸዉ» አዝማሪ ከየት ወዴት » በተሰኘ ርዕስ የአዝማሪን ሥራ ለማኅበረሰቡ የሚሠጠዉን ጠቀሚታ በተመለከተ በባሕር ዳር ዩንቨርስቲ የሁለት ቀናት አዉደ ጥናት ላይ ተሳታፊ የነበሩት አዝማሪ ነጋ ሙሉዓለም አደገና ባለቤታቸዉ ምግብ ካዜሙት ተወሰደ ስንኝ ነዉ። ጤና ይስጥልኝ አድማጮች እንደምን ሰነበታችሁ ስንኝ ቋጣሪዉ፤ ግጥም ደራሲዉ፤ መሰንቆ ተጫዋቹ፤ አንድ እሱ ራሱ ድምፃዊም ሆኖ እንደ አንድ ሙዚቃ ባንድ ስለሚያገለግለዉ ስለአዝማሪ ሥራ እያወሳን የባሕር ዳሩ የአዝማሪ ጉባዔ እንቃኛለን።