1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አዉሮጳና ጀርመን

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 29 2001

ምጣኔ-ሐብቱ ያንሰራራል-የሚል የሩቅ ተስፋ ሰሞኑን መሰማቱ አልቀረም። ተስፋዉ ግን በቅርቡ ተሰብስበዉ የነበሩት የአዉሮጳ የገንዘብ ሚንስትሮች እንዳሉት በተለይ የሥራ አጡን ቁጥር ይጨምራል የሚል ሥጋት አልተለየወም

https://p.dw.com/p/HlRL
ኢንተርኔትና የግለሰብ መረጃምስል www.hfp.mhn.de
ጤና ይስጥልኝ እንደምን ዋላችሁ።የዛሬዉ አዉሮጳና ጀርመን ዝግጅታችን እሁለት የሚከፈሉ ሰዎስት ጉዳዮች ይዳሰሱበታል።አለምን የመታዉ የምጣኔ ሐብት ድቀት የዕለት-ከዕለት ርዕሥ-ሥጋትም በሆነበት ዘመን-አሁን ምጣኔ-ሐብቱ ያንሰራራል-የሚል የሩቅ ተስፋ ሰሞኑን መሰማቱ አልቀረም። ተስፋዉ ግን በቅርቡ ተሰብስበዉ የነበሩት የአዉሮጳ የገንዘብ ሚንስትሮች እንዳሉት በተለይ የሥራ አጡን ቁጥር ይጨምራል የሚል ሥጋት አልተለየወም።እንደምጣኔ ሐብቱ ድቀት ሁሉ የዜጎች የግል መረጃና ሚስጥርን የመጠበቅ መብት ቢያንስ ለጀርመናዉያን አነጋጋሪ ሆኖ-ነዉ የሰነበተዉ።ሁለቱ-ርዕሶች የዝግጅታችን የመጀመሪያ ክፍል ትክረት ናቸዉ።ማንተጋፍቶት ሽለሺ አጠናቅራቸዋል።
Symbolbild Europäische Union beim G20 Treffen in London
የምጣኔ-ሐብት ኪሳራና የአዉሮፓ ሕብረትምስል DW/AP/dpa


ሁለተኛዉ ርዕሥ ወደ ለንደን ያጉዘኛል።ብሪታንያ የሚኖሩና የሚሠሩ የዉጪ ሥደተኞች፥ ሲሆን ዜግነት ይሕ ቢቀር ሕጋዊ የመኖሪያ ፍቃድ እንዲሰጣቸዉ ባለፈዉ ሰኞ በሰልፍ ጠይቀዋል።ሃያ-ሺሕ የሚገመት ሥደተኛና የስደተኞች መብት ተሟጋቾች የተካፈሉበትን ሠልፍ ያደረጀዉ ለስደተኞች የሚቆረቆር ማሕበር ነዉ።የለንደንዋ ወኪላችን ሐና ደምሴ የሰልፈኛዉን ጥያቄ፥ እና የሰልፉን ሂደት ተከታትላዉ ነበር።