አወዛጋቢው የኢትዮጵያ አውሮፕላን አደጋ መንስኤ3 የካቲት 2002ረቡዕ፣ የካቲት 3 2002ከሁለት ሳምንት በፊት ከቤይሩት ሊባኖስ ሲነሳ ከነ መንገደኞቹ የወደቀው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አደጋ መንስኤ አሁንም እያወዛገበ ነው የሊባኖስ ባለስልጣናት የአደጋው ምክንያት መጥፎ አየር ነው ሲሉ ስማቸው ያልተጠቀሰ ወገኖች ደግሞ መንስኤው የፓይለቱ ስህተት ነው እያሉ ነው ።https://p.dw.com/p/LyGoስመጥሩዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድምስል APማስታወቂያምርመራው አሁን አልተጠናቀቀም ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በበኩሉ የምርመራውን ውጤት መጠበቅ አለብን ባይ ነው ። ሸዋዪ ለገሰ የአየርመንገዱን የአደጋ ተከታታይ ግብረ ኃይል አስተባባሪ ካፕቴን ደስታ ዘሩን አነጋግራለች ። የአደጋው መንስኤ የፓይለቱ ስህተት ነው ለተባለው ካፒቴን ደስታ ዘሩ መልስ በመስጠት ይጀምራሉ ። ሸዋዬ ለገሠ ሂሩት መለሠ