አካባቢን ለመከባከብ የኅብረተሰብ ጥረት
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 20 2003ማስታወቂያ
በሃረማያ ሐይቅ ላይ የገጠመዉ የመድረቅ አደጋም በስምጥ ሸለቆ አካባቢ በሚገኙ ሐይቆች ላይ በተመሳሳይ ሁኔታ እያንዣበበ መሆኑን ጥናት ያካሄዱ ባለሙያ በሳምንታዊ ጤናና አካባቢ ዝግጅታችን ቀርበዉ ማብራራታቸዉ ይታወሳል። በኦሮሚያ ክልል ፤ በምሥራቅ ሸዋ ፣ ጋሎ አረጲ በተባለ ሥፍራ የተፈጥሮ አካባቢን መራቆት ለመቋቋም፣ ኅብረተሰቡ የሚያደርገውን ጥረት ፣ እንዲሁም ድርቅ በዐቢያታ ሀይቅ ላይ ያስከተለውን ከባድ ተጽእኖ ከሰሞኑ ተመልክቶ የተመለሰው የአዲስ አበባው ዘጋቢአችን ጌታቸው ተድላ፣ የሚከተለውን ዘገባ ልኮልናል።