አስቂኝ የፍቅር ፊልሞች በኢትዮጵያ
ዓርብ፣ ግንቦት 10 2004ማስታወቂያ
«ወጣቶች እና በፍቅር ዙሪያ የሚያጠነጥኑ አስቂኝ ፊልሞች በኢትዮጵያ መበራከት» የዛሬው የወጣቶች ዓለም መሰናዶ ርዕሳችን ነው። ለመሆኑ በኢትዮጵያ የሚገኙ አብዛኞቹ ፊልም ሰሪዎች የዚህ አይነቱ የፊልም ዘውግ ላይ ማተኮር የፈለጉት ለምንድን ነው? በተዋናይነት፣ በአዘጋጅነት እና በዩኒቨርሲቲ መምህርነት የሚንቀሳቀሱ ሶስት ወጣቶች የሚሉት ይኖራል።
የፊልም ስራ እንደሌላው የጥበብ ዘርፍ ሁሉ በቅርፅ፣ በይዘት እና በአይነት ፈርጀ-ብዙ የሆነ ዘውግ ያካተተ ጥበብ ነው። በድርጊት የተሞላ አክሽን ፊልም፣ ገድልን መሰረት ያደረገ አድቬንቸር፣ ወንጀል ነክ፣ ታሪካዊ፣ አስቂኝ፣ ፍርሀትን አጫሪ፣ ድራማ፣ ሳይንሳዊ ልብ ወለድ፣ የጦርነት ፊልም እና ሙዚቃዊ ፊልም እያሉ ዘውጎችን መከፋፈል ይቻላል። ይሁንና ግን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሰሩ ፊልሞች ባብዛኛው ከዚህ ሁሉ ዘውግ አስቂኝ ፊልሞችን የሙጥኝ ያሉ ይመስላል፤ በተለይ ደግሞ አስቂኝ የፍቅር ፊልሞችን። ግን ለምን...?
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አርያም ተክሌ