አሜሪካ የመሪነት ሚናዉን ዉሰጂ!
ማክሰኞ፣ ኅዳር 1 2002ማስታወቂያ
ለአየር ጠባይ መለወጥና ለዓለም የሙቀት መጨመር ምክንያት የሆኑትን በካይ ጋዞች ለመቀነስ በሚል ከዓመታት በፊት በጃፓን ኪዮቶ ላይ በመንግስታት የተፈረመዉ የኪዮቶ ዉል የሚያከትምበት ወቅት እየደረሰ ነዉ። ያንን ያዉም አደገኛ ከባቢ አየር በካይ መሆናቸዉ የሚታወቀዉ አገራት ያልፈረሙበት ዉል በሌላ እንዲተካ የተጀመረዉ ጥረት የኮፐንሃገኑ ጉባኤ ከመድረሱ በፊት እጅግም ተስፋ ሰጪ ምልክት ባለመታየቱ የአካባቢ ተፈጥሮ ተቆርቋሪዎች ዛሬም በየአገሩ ድምፃቸዉን ማሰማት ቀጥለዋል። ሰሚ ጆሮ ካገኘ ጥቅሙ የጋራ ነዉና በኢትዮጵያ ለተጀመረዉ ዘመቻ ፊርማችንን በማኖር በአየር መዛባት ለሚቸገረዉ ወገናችን አጋርነታችንን እናሳይ።
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ