1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ንዋዬ ቅድሳት ለማስጠበቅ የሚጥር ማኅበር፣

ሰኞ፣ ሐምሌ 22 2005

የኢትዮጵያን አብያተ ክርስቲያን ንዋዬ ቅድሳትና የተለያዩ ቅርሶችን በሥርዓት ለመጠበቅ ባለመቻሉ፣ የሚያስጠብቅም ባለመኖሩ ፣ ባለፉት አያሌ ዓመታት እጅግ በዛ ያሉ ንዋዬ ቅድሳትና የተለያዩ የቤተክርስቲያኒቱ ቅርሶች ወደ ውጭ እየተጋዙ ገበያ ላይ መዋላቸው እንግዳ ነገር አልሆነም።

https://p.dw.com/p/19GkU
ምስል DW/A.Tadesse-Hahn

ከዚህ ቀደም ለቅርስ ጥበቃ ቆመናል የሚሉ ድርጅቶች ባይታጡም፣ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅርሶች እንክብካቤና ልማት ማኅበር የተሰኘ አንድ ሌላ አዲስ ድርጅት መመሥረቱን ጌታቸው ተድላ ኃ/ጊዮርጊስ የላከልን ዘገባ ያስረዳል። አዲሱ ማኅበር፤ አዲስ አበባ ውስጥ በኢንተር- ኮንቲኔንታል ሆቴል ባዘጋጀው የምክክር መድረክ፤ በህገ ወጥ መንገድ ቅርሶች ከሀገር የሚወጡበት ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ለይ መድረሱን ጥናት ያካሄዱ ምሁራን ገልጸዋል።

ጌታቸው ተድላ ኃ/ጊዮርጊስ

አርያም ተክሌ