«ኑሮን እንዳውቅ ወደ ኢትዮጵያ ተላኩ»
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 12 2005ማስታወቂያ
የሶስት አመት ልጅ ሳለ ከቤተሰቦቹ ጋ ወደ ዮናይትድ እስቴትስ ይሄዳል። ኑሮውም እዛው ይሆናል። ለቤተሰቦቹ ግን ምትኩ የሚመኙትን አይነት ልጅ አልሆነላቸውም። «በልጅነቴ አስቸጋሪ ልጅ ነበርኩ» ይላል ዛሬ። 4ኛ ክፍል እስኪደርስ ድረስ እንዲስተካከል ቤተሰቦቹ ብዙ ጣሩ። ችግሩን ማቃለል ግን አልቻሉም። ስለሆነም ወደ ኢትዮጵያ ላኩት።
ከ12 ዓመታት የኢትዮጵያ ቆይታ በኋላ ምትኩ ተመልሶ በዮናይትድ እስቴትስ ኑሮውን ቀጥሏል። ፀባዬን ለማሳመር ይህን ያህል ጊዜ ፈጅቶብኝ አይደለም ይላል። ምትኩ ሲመለስ ኑሮ በዮናይትድ እስቴትስ አልከበደውም ። የኢትዮጵያ ኑሮው ኃላፊነትንና ቁርጠኝነትን አስተምሮታል።
ታሪኩን አካፍሎናል። ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።
ልደት አበበ
ነጋሽ መሐመድ