ቴክኖሎጂና ወጣት አካል ጉዳተኞች
ዓርብ፣ መጋቢት 27 2005በተለይ በምዕራቡ አለም አካል ጉዳተኞች ቴክኖሎጂን ተጠቅመው ህይወታቸውን ልክ እንደ ማንኛውም ሰው ሲመሩ ይስተዋላል። ጋዜጠኛ ቴድሮስ አይነ ስውርም ስለሆነ ጉዳዩን በቅርበት ይከታተላል።
ቴድሮስ ለአይነ ስውራን የሚሆኑ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ሲወጡ እየተከታተለ አጠቃቀማቸውንም ይሞክራል። ሀገሪቷ ባላት የቴክኖሎጂ አቅርቦት ልክ፣ የገንዘብ እና የአስተሳሰብ አቅም አካል ጉዳተኞች የቴክኖሎጂው ተጠቃሚ እንደሆኑ ቴድሮስ ይናገራል። ይሁንና ኢትዮጵያ ውስጥ በአጠቃላይ ለአካል ጉዳተኞች ጠቃሚ የሚባለው ቴክኖሎጂ ምንም ያህል እንዳልተስፋፋ ነው የሚናገረው።
አይነ ስውራን ኢንተርኔት በመጠቀም አዲስ ስለሚወጡ ቴክኖሎጂዎች፣ እና ስልቶች ከሌሎች በአለም ዙሪያ ካሉ ፤ማየት ከማይችሉ እና ከሚችሉ ሰዎች ጋ ሀሳብ መለዋወጥ ይችላሉ። ለምሳሌ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ አይነ ስውራን እየተማሩት ስላለው
የክሊክሶናር የድምፅ አወጣጥ ስልት። የሚያስተጋባውን የገዛ ድምፃቸውን መልሰው በማስተዋል ከግንብ ፣ዛፍ እና ሌሎች ነገሮች ፊት ቆመው እንደው መለየት ይችላሉ።
ቴክኖሎጂ አይነ ስውራንንም ይሁን ሌሎች አካል ጉዳተኞች ጥገኛ ሳይሆኑ እንዲንቀሳቀሱ መንገድ ቢፈጥርም፤ በአግባቡ ያለማስተዋሉ ሁኔታ፤ እንኳን ጉዳተኞችን ማንኛውንም ሰው አደጋ ውስጥ የሚጥሉ ናቸው። ወደፊት በአካል ጉዳተኞች ላይ በማወቅ ወይንም ባለማወቅ የሚፈፀሙት የመብት ጥሰቶች እንዲቆሙ ምን መደረግ አለበት? ለመብት ጥሰቱ መንስኤ የአመለካከት ችግር እንደሆነ ቴድሮስ ያስረዳል።
ቴክኖሎጂ ለወጣት አካል ጉዳተኞች ስለሚጫወተው ሚና ከጋዜጠኛ ቴድሮስ ፀጋዬ ጋ በወጣቶች አለም ያደረግነውን ቆይታ ከዚህ በታች ማድመጥ ይቻላል።
ልደት አበበ
አርያም ተክሌ