ታቅዶ የከሸፈዉ የስልጣን ሽግግር በየመን
ሐሙስ፣ ግንቦት 11 2003ማስታወቂያ
ስምምነቱ ምንም እንኳን ፕሬዝደንት አሊ አብደላ ሳልህን ያለመከሰስ መብት አስከብሮ በክብር ከስልጣን መንበር የሚነሱበትን መንገድ ያመቻቻል ተብሎ ቢታሰብም ዘገባዎች እንዳመለከቱት ሳልህ ፈቃደኛ ባለመሆናቸዉ ሳይፈረም ቀርቷል። ስምምነቱን ያመቻቹት የባህረ ሰላጤዉ ሀገራት ምክር ቤት ሚኒስትሮች በመጪዉ ቀናት ዳግም ሪያድ ላይ እንደሚሰበሰቡ ሲገለፅ የመናዉያን ተደራዳሪዎቹ ይገኙ እንደሁ ግን የተገኘ መረጃ የለም። ይህ በእንዲህ እንዳለም የአሜሪካን ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ በየመን የስልጣን ሽግግር እንዲደረግ አሳስበዋል። ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት የፊታችን እሁድ በየመን ተቀናቃኝ ወገኖች መካከል ለሁለተኛ ጊዜ ተሞክሮ የከሸፈዉ ስምምነት ሊፈረም ይችላል።
ነብዩ ሲራክ
ሸዋዬ ለገሠ
ሂሩት መለሠ