ተጨማሪ የርዳታ ጥሪ ለኢትዮጵያዉያን
ሐሙስ፣ የካቲት 3 2008ማስታወቂያ
ኢትዮጵያን በመታዉ ድርቅ ለረሐብ ለተጋለጠዉ ሕዝብ መርጃ ተጨማሪ እርዳታ እንዲሰጥ ዓለም አቀፉ የሕፃናት መርጃ ድርጅት ሴቭ ዘ ችልድረን ተማፀነ።ለምግብ እጥረት ለተጋለጠዉ ከአሥር ሚሊዮን ለሚበልጠዉ ኢትዮጵያዊ መርጃ ለጋሾች 1,4 ቢሊዮን ዶላር እንዲሰጡ የኢትዮጵያ መንግሥት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በቅርቡ ጠይቀዉ ነበር።የሴቭ ዘ ችልድረን ሐላፊዎች አሁን እንዳስታወቁት ለችግረኛዉ ምግብ ለማቅረብ የ245 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ ርዳታ ባስቸኳይ ያስፈልጋል።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ አለዉ።
ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ