1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ተገን ጠያቂዎች እና የጀርመን የስለላ መስሪያ ቤት

ዓርብ፣ ኅዳር 13 2006

ጀርመን እንድትቀበላቸው ያመለከቱ ተገን ጠያቂዎች ማመልከቻቸው ተቀባይነት እስኪያገኝ ረዥም ጊዜ በሚወስድ ሂደት ውስጥ ማለፍ አለባቸው ። ጉዳዩ የሚመለከታቸው የፌደራል ጀርመን የውጭ ዜጎችና የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ባልደረቦች አመልካቾቹን ስለ ሃገራቸው ሁኔታ ና የፖለቲካ ክትትል ይደረግባቸው እንደሆነ ይጠይቋቸዋል ።

https://p.dw.com/p/1AMhC
Dolmetscher Ahmed Yasser spricht am 10.10.2013 in einem Büro in der Außenstelle des Bundesamts für Migration und Flüchtlinge in Berlin-Spandau mit Asylbewerbern aus Syrien . Foto: Bernd von Jutrczenka/dpa
Beratung für Asylbewerberምስል picture-alliance/dpa

በምን ዓይነት መንገድ ወደ ጀርመን ሊመጡ እንደቻሉም ያጣራሉ ። ይህ የተለመደና በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የሚታወቅ አሠራር ነው ። ይሁንና በዚህ ሂደት የጀርመን ህዝብ እንኳን የማያውቃቸው ሌሎች ባለሥልጣናት በዚህ ሂደት ውስጥ እንደሚሳተፉ የዶቼቬለው የቮልፍጋንግ ዲክ ዘገባ ያስረዳል ።

መቀመጫውን በጀርመን ዋና ከተማ በርሊን ያደረገው የውጭ ዜጎችን የሚመለከቱ ጉዳዮችን የሚቆጣጠረው የፊደራል ጀርመን መሥሪያ ቤት በይፋ በመራሄ መንግሥት ጽህፈት ቤት ስር የሚገኝ ተቋም ነው ። ተቋሙ እጎአ ከ 1958 ዓም አንስቶ ለጀርመናውያን ደህንነት አስፈላጊ የሆኑ ለጀርመን የስለላ መስሪያ ቤት የሚጠቅሙ መረጃዎችን ይሰበስባል ። ዙድ ዶይቸ ሳይቱንግ የተባለው ጋዜጣና NDR የተባለው የጀርመን ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች በጋራ እንደዘገቡት የዚህ ተቋም የሥራ ባልደረቦች ተገን ጠያቂዎች በሃገራቸው የአሸባሪ ድርጅቶች አባላትን ያውቁ እንደሆነ ወይም ደግሞ የጦር መሣሪያ ስለሚደበቁባቸው ቦታዎች የሚያውቁት እንዳለ ይጠይቁዋቸዋል ። በፅንሰ ሃሳብ ደረጃ እነዚህ መረጃዎች ለጀርመን የስለላ መስሪያ ቤት ተላልፈው አሸባሪዎችን በሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት ለመግደል ሊውሉ ይችላል ። ጀርመን ውስጥ ለተገን ጠያቂዎች ጥብቅና የሚቆሙ በርካታ ጠበቆች እነዚህን ባለሥልጣናት ያውቃሉ ። ቪክቶር ፋፍ ፍራንክፈርት ውስጥ ከ40 ዓመታት በላይ የተገን ጠያቂዎች ጠበቃ በመሆን ሰርተዋል ። ከበርሊኖቹ ባለሥልጣናት ጋርም በግል ተነጋግረዋል ። ፋፍ እንደሚሉት ሠራተኞቹ ትሁትና ግልፅ ናቸው ። ከፌደራል ጀርመን የስለላ መስሪያ ቤት ጋር ግንኙነት እንደሌላቸውም ነው የሚናገሩት ።

Rechtsanwalt Pfaff. Er ist spezialisiert auf alle Rechtsfragen, die Unionsbürger und Ausländer betreffen, unter anderem: EU-Migrations- und Ausländerrecht Staatsangehörigkeitsrecht Asyl- und Flüchtlingsrecht Arbeitsgenehmigungsrecht Berufszulassungsrecht Strafverteidigung mit ausländerrechtlichem Bezug Rechte geklärt
ፋፍምስል RA Pfaff


«ከፌደራል የስለላ መስሪያ ቤት ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌላቸው ነው የሰማሁት ። ለመራሄ መንግሥት ጽህፈት ቤት ዘገባ እንደሚያቀርቡ ና እዚያ የሚገኙትም ለጽህፈት ቤቱ ጠቃሚ ሊሆኑ ይችላሉ ብለው የሚያስቧቸውን አንዳንድ መረጃዎች ለማግኘት መሆኑን ነው በቀጥታ የተነገረኝ ። »
የጀርመን የስለላ መስሪያ ቤትም በመራሄ መንግሥቱት ቢሮ ስር ነው ። ፋፍ እንደሚሉት በ40 ዓመት የአገልግሎት ዘመናቸው ቃለ መጠይቅ በመደረጌ ችግር ገጥሞኛል ያላቸው ተገን ጠያቂ አላጋጠማቸውም ። በተቃራኒው ፋፍ አንዳንዴ የተገን ጠያቂዎች ማመልከቻዎች አፋጣኝ መልስ እንዲያገኙ የመስሪያ ቤቱን ባልደረቦች ያነጋግራሉ ። ደንበኞች ለዚህ መሥሪያ ለስለላው መሥሪያ ቤት ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን መስጠት ከቻሉ በጥቂት ቀናት ውስጥ የመኖሪያ ፈቃድ ያገኛሉ ። እንደዚህ ዓይነት ስምምነቶች ላይ የሚደረሰው ግን ሁሌም አይደለም ። መረጃዎችን ሳያሳውቁ መሰብሰብም ሊኖር ይችላል ። በአንዳንድ ሁኔታዎች ደግሞ አደገኛ ሊሆንም ይችላል ይላሉ ።

Asylsuchende vor dem Gebäude der zentralen Aufnahmestelle für Asylbewerber in Berlin.
ተገን ጠያቂዎች በበርሊንምስል Nikita Jolkver

« አደገኛ ሊሆን የሚችለው የውጭ የስለላ ድርጅቶች ተገን ጠያቂዎቹ የሚሰጡትን መረጃ ማወቅ ከፈለጉ ነው ። ይህ ግን ሁሌም የሚሆን አይደለም ። »
ፋፍ እንደሚሉት ይህ የሚደረግ ከሆነ ተገን ጠያቂዎች መጠቀሚያ እንደሆኑ ሊሰማቸው ይችላል ። እነዚህን ስለመሳሰሉ ጉዳዮች መስማታቸውን የሚናገሩት ፋፍ በርሳቸው እምነት ይህን መሰሉ አሰራር አደገኛ ነው ። ምክንያቱም በርሳቸው አስተያየት አሸባሪዎች በክህደት የሚጠረጥሩዋቸውን በዚያው ተገን በጠየቁባቸው ቦታዎች ሊበቀሉዋቸው እና ሊገድሏቸውም ይችላሉ ።

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ