ብሪታንያ ርዳታዋን ተቀባይ ሀገራትን መቀነሷ
ሐሙስ፣ የካቲት 24 2003ማስታወቂያ
ብሪታንያ በምታደርገዉ ርዳታ ላይ መሠረታዊ ለዉጥ ለማድረግ መዘጋጀቷን ያመለከተች ሲሆን ከእንግዲህ ርዳታዉ አይስፈልጋቸዉም በሚል ከተቀነሱት 16 ሀገራት መካከል ቻይና፤ ሩሲያ፤ ቪየትናም፤ ሞልዶቪያ፤ ካሜሮን፤ ኮሶቮ፦ ኢራቅና ሰርቢያ ይገኙበታል። ወደፊት የብሪታንያ ርዳታ በ27 የድሃ ድሃና በቋፍ ያሉ በተባሉ አገሮች ላይ ብቻ እንደሚያተኩር ሲገለፅ አፍጋንኒስታን፤ ባንግላዴሽ፤ ዴሞክራቲክ ኮንጎ፤ ኢትዮጵያ፤ ህንድ፤ ፓኪስታን፤ ሶማሊያ፤ ሱዳን የመንና ዚምባብዌ ርዳታ እንደሚያገኙ ተገልጿል።
ሃና ደምሴ
ሂሩት መለሠ