1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ቤን አኩር ቱኑዝያዊው የዲሞክራሲ ተሸላሚ

ሐሙስ፣ ጳጉሜን 1 2004

ቱኒዝያዊው የህግ ባለሞያ ያድ ቤን አኩር እዚህ ቦን ውስጥ አለም ዓቀፍ የዲሞክራሲ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ። ቤን አኩር እጎአ ከጥር 2011ቱ የቱኒዝያ ህዝባዊ አብዮት በኋላ የመጨረሻው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ያበቃው የቱኒዝያ የተሃድሶ ኮሚሽን ሃላፊ ነበሩ ።

https://p.dw.com/p/164dE
GettyImages 111657888 Yadh Ben Achour, professor of law at the Tunis University, sits in his office in Tunis on March 12, 2011. Yadh Ben Achour is preparing the architecture for tomorrow's Tunisia by preparing and electoral law and the futur constitution. AFP PHOTO / FETHI BELAID (Photo credit should read FETHI BELAID/AFP/Getty Images)
ምስል Getty Images

ቱኒዝያዊው የህግ ባለሞያ ያድ ቤን አኩር እዚህ ቦን ውስጥ አለም ዓቀፍ የዲሞክራሲ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ። ቤን አኩር እጎአ ከጥር 2011ቱ የቱኒዝያ ህዝባዊ አብዮት በኋላ የመጨረሻው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድ ያበቃው የቱኒዝያ የተሃድሶ ኮሚሽን ሃላፊ ነበሩ ። ቤን ለዚህ ሽልማት የበቁት የቱኒዝያው ለውጥ እንዲሳካ ላደረጉት አስተዋፅኦ ነው ። የዶቼቬለዋ ሳራ ሜርሽ ያቀረበችውን ዘገባ ሂሩት መለሰ አጠናቅራዋለች ።

እጎአ ጥር 14 2011 አም ምሽት ላይ የየቀድሞው የቱኒዝያ ፕሬዝዳንት ሲን አል አቢዲን ቤን አሊ ሃገሪቱን ጥለው መውጣታቸውን ሲሰሙ ያድ ቤን አኩር ከት ብለው ነበር የሳቁት ። በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን በፌስ ቡክ የተነዛ ወሪ ነበር የመሰላቸው ። ለ 23 አመታት ቱኒዝያን በብረት ጡጫ የገዙት አምባገነኑ መሪ እንዲህ በአንዴ ይጠፋሉ ብለው አላሰቡም ነበር ። ከጥቂት ቀናት በኋላ የህግ ባለሞያው ቤን አኩር በቱኒዝያ የፖለቲካ ተሃድሶ እንዲያካሂድ በተቋቋመው ኮሚሽን ውስጥ ተሰየሙ ። ወደ ስራ የገቡትም በደስታና በትጋት በበቱኒዝያ በአፋጣኝ ዲሞክራሲ የማስፈን ተስፋ ጨብጠው ነበር ።

Professor Yadh Ben Achour (Mitte), Präsident der ersten verfassungsgebenden Kommission Tunesiens, ist am 06.09.2012 mit dem Internationalen Demokratiepreis Bonn ausgezeichnet worden. Rechts im Bild DW-Intendant Erik Bettermann, Vorsitzender des Vereins Internationaler Demokratiepreis Bonn, beim Pressegespräch. Links im Bild Jürgen Nimptsch, Oberbürgermeister von Bonn.
ምስል Barbara Frommann

« ግብታዊ አብዮት ነበር ። ግርማ ሞገስ ባለው መሪ ሳይሆን ነፃነትና ዲሞክራሲ በጠየቁ ወጣቶች ነበሩ የሚመራው ። መልእክታቸው ዘመናዊነት ነበር ። ይህ አብዮት ከዚህ ቀደም ዲሞክራሲ የምእራባውያን ግኝት ነው የሚለውን የኖረ አስተሳሰብ አስወግዷል ። የሆነው ሁሉ ካለ አንዳች የውጭ ጣልቃ ገብነትነት ነው የተከናወነው ። »

በመሰረቱ የቤን አኩርና የኮሚሽኑ ባልደረቦች እቅድ የቀድሞውን የቱኒዝያ ህገ መንግሥት ማሻሻል ነበር ። ሆኖም ከህዝቡ በኩል ግፊቱ ከፍተኛ ነበርና አዲስ የህግ ስርዓት መዘርጋት የግድ ሆነ ። በመጨረሻም ጊዜያዊው መንግሥት ተስማምቶ እጎአ ጥቅምት 2011 በቱኒዝያ የመጀመሪያው ነፃ የህዝብ ተወካዮችና የህገ መንግሥት አርቃቂ ምክር ቤት ምርጫ ተካሄደ ። ቤን አኩር የሚመሩት ኮሚሽን ግን በዚህ ተግባር ብዙም አልተሳተፈም ። ያም ሆኖ በሚቀጥለው አመት አጋማሽ ላይ ህገ መንግግስቱ ተረቆ ያበቃል የሚል ግምት አለ ። ቤን አኩር ግን በተስፋ ና በቀቢፀ ተስፋ መካከል ናቸው ።

«በዲሞክራሲያዊ ህይወት ውስጥ የመጀመሪያዎቹ እርምጃዎች ሁሌም በስኬት የተሞሉ ላይሆኑ ይችላሉ ። አጠቃላዩን ሥርአት ከመሠረቱ ነው የምንገነባው ። ዲሞክራሲያዊ ባህል ያለን የአውሮፓ አገር አይደለንም ። ይሁንና ሀ ብለም እንጀምራለን ።»

የቱኒዝያው አብዮት ከተካሄደ ከ 18 ወራት በኋላ የ67 አመቱ የ የቤን አኩር የቀድሞው ተነሳሽነት ቀንሷል ። ከአብዮቱ ወዲህ የቱኒዝያ የፖለቲካ ገፅታ እየተካረረ ሄዷል ። በተደጋጋሚ ጊዜያት የግራ መስመር ተከታዮችና ወግ አጥባቂ ኃይሎች ግፊት ያደርጋሉ ። የተለያዩ ፓርቲዎች የተሰባሰቡበት የሽግግሩ መንግሥት አብዛኛው ሥልጣን አንሃንዳ የተባለው የሙስሊም ፓርቲ ነው ። ይህ ፓርቲ ደግሞ በአብዮቱ ሳይሳተፍ በየትኛውም መንገድ ሃይማኖታዊ አጀንዳውን ተግባራዊ ለማድረግ የሚንቀሳቀስ ፓርቲ ነው እንደ ቤን አኩር ።

epa02638713 Tunisian professor of law at the Tunis University, Yadh Ben Achour speaks during a meeting of the Council of the Tunisian Revolution in Tunis, Tunisia on 17 March 2011. Yadh Ben Achour is preparing the architecture for tomorrow's Tunisia by preparing and electoral law and the futur constitution. EPA/STR +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

« የምርጫው ውጤት ከአብዮቱ መንፈስ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም ። በተቃውሞው ወቅት አንድም ሃይማኖታዊ መፈክር አልነበረም »

በቤን አኩር ቤተሰብ ፖለቲከኝነት የነበረ ነው ። አባታቸው የሰራተኞች ማህበር መሪ ፣ የህግ ባለሞያ ና ከዚህም በላይ የቱኒዝያውያን ሙፍቲ ነበሩ ። ወጣቱ ያዶህ በሃገራቸው በቱኒስያ ህግ አጥንተው በፓሪስ ፈረንሳይ ደግሞ በህግ የዶክትሬት ዲግሪ አግኝተዋል ። እምብዛም በፖለቲካው ተሳታፊ ያልሆኑት ቤን አኩር ለመጀመሪያ ጊዜ እጎአ በ 1987 ቤን አሊ ሥልጣን ሲይዙ ነበር የህገ መንግሥት ምክር ቤት ውስጥ መስራት የጀመሩት ። እጎአ በ1992 ፀረ ዲሞክራሲ የሆኑትን ህገ መንግስታዊ ድንጋጌዎች በመቃወምም ሥራቸውን በፈቃዳቸው ለቀቁ ። ወደ ፖለቲካው የተመለሱት ከቱኒዝያው አብዮት በኋላ ነው ። በቤን አኩር እምነት እስልምናና ዲሞክራሲ በትክክል አብረው መጓዝ ይችላሉ ። ሃገራቸው ቱኒዝያም ይህን መንገድ እንድምትከተል ተስፋቸው የፀና ነው ።

ሂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ